Online Admission "በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ በዓላትን በጋራ እናክብር " በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ከሰልጣኞች እና ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደረገ::

"በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ በዓላትን በጋራ እናክብር " በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ከሰልጣኞች እና ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደረገ::

25th September, 2025

    በለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የመስቀል እና ለኢሬቻ በዓል ለማክበር "በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ በዓላትን በጋራ እናክብር " በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ሰነድ ከሰልጣኞች እና ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተደረገ::

ቀን: 14/01/2018 ዓ.ም

የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን

    የመስቀል እና የኢሬቻ ለማክበር በ ለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ውይይት የተደረገ ሲሆን የመወያያ ሰነዱን የኮሌጁ ዋና ዲን ታደሰ መኮንን (ዶ/ር) አቅርበዋል::

    በመድረኩ ሀገራችን ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መኖሪያ፤ የብዝሀ ሀይማኖቶች ማህደር፤ የአብሮነት እና የመቻቻል አብነት እና ብልጽግናን እውን ለማድረግ የምትታትር የብዝሀ ጸጋ ምድር ስትሆን ህዝቦቿም በብዝሃነታቸዉ ውስጥ የጠነከረ አንድነትን በማፅናት የሚያጋጥሟቸዉን ፈተናዎች በተባበረ ክንድ በማሸነፍ እዚህ የደረሱ ጀግና መሆናቸው በአለም ደረጃ የማግካድ ሀቅ መሆኑ በውይይቱ በዝርዝር ተነስቷል። 

    ስለሆነም ባዓላቱ ተጀምረው እስኪጠናቀቁ ያላቸውን ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴት ጠብቀው በሰላም ተጀምረው በሰላም እንዲጠናቀቁ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀላፊነት መሆኑን መግባት ላይ ተደርሷል፡፡ 
ከውይይቱ በኋላ ባዕለቱን ምክህት በማደረግ የአብርነትና የመልካም በዓል መግለጫ የሚሆን የዳቦ ቆረሳ ፕሮግራም በኮሌጁ አመራሮች ተካሂዷል::

የለሚ ኩራ ማኑራክቸሪንግ ኮሌጅ

.

Copyright © All rights reserved.

Created with