Online Admission የለሚ ኩራ ማኑፋቸሪንግ ኮሌጅ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ስር ያሉ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡

የለሚ ኩራ ማኑፋቸሪንግ ኮሌጅ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ስር ያሉ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡

19th August, 2025

የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ስር ያሉ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ  የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡


    በለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ነሃሴ 13/12/2017 ዓ/ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ስር ያሉ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰና መምህራን የክፍለ ከተማ አመራሮች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የውይይት መድረክ ተካሄዷል፡፡
መድረኩን የመሩት የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት አይናለም የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ እና የጋራ ስራዎችን በጋራ ለመስራት ያለመ የውይይት መድረክ መሆኑን ገልፀዋል፡፡


     የኮሌጁ ዋና ዲን ታደሰ መኮንን (ዶ/ር) የኮሌጁን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሰልጣኝ ቅበላ እና የንቅናቄ እቅድ ሰነድ በማቅረብ ዝርዝር ማብራሪያና ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከመድረኩ ለሚነሱ ጥያቄዎች ከወ/ሮ ለሊሴ ጋር በመሆን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡


   በተጨማሪም የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ ልማት ም/ዲን የሆኑት ሙሉጌታ አለሙ (ዶ/ር) ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎች ተጨማሪ ማብራሪያ በመስጠት ኮሌጁ በ2018 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር  በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡ እንዲሁም የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት አይናለም የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ በሚዘጋጀው ትግበራ መሰረት የ2018 ዓ.ም  እቅድ ማሳካት እንደሚቻል  ገልፀዋል፡፡


    በመጨረሻም  ኮሌጁ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ስር ያሉ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካከል የ2018 ዓ.ም የሰልጣኝ ቅበላ በጋራ ለመስራት የትብብር ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡


ለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ  ኮሌጅ 
ነሃሴ 13/12/2017 ዓ/ም

.

Copyright © All rights reserved.

Created with