Online Admission የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2018 የሰልጣኞችን ቅበላ አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ

የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2018 የሰልጣኞችን ቅበላ አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ

07th November, 2025

የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2018 የሰልጣኞችን ቅበላ አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ
የለሚ ኩራ ማኑፋክቼሪንግ ኮሌጅ ከለሚ ኩራ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት እንዲሁም ከህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በ2018 የሰልጣኞችን ቅበላ አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል።
በውይይቱ የኮሌጁን ነባራዊ ሁኔታ፣የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አስፈላጊነትና የተማሪዎች ቅበላ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች አስመልክቶ ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን ተማሪዎች ወደ ኮሌጁ ገብተው መማር እንዲችሉ የሚመለከታቸው ባለድርሻ እስከ ብሎክ ድረስ ወርደው የቅስቀሳ ስራ በመስራት ወጣቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑና የቀረበውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ቤዛ ደመቀ ቴክኒክና ሙያ ሀገርን የሚለውጡ ዜጎችና የሚሰሩ እጆች የሚገነቡበት ተቋም በመሆኑ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መስራትና ተማሪዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ የንቅናቄ ስራ መሰራት አለበት ብለዋል።
የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ታደሰ ኮሌጁ በ2018 ተማሪዎችን በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በልዩ ልዩ የትምህርት ዘርፎች ተቀብሎ ለማሰልጠን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጸው ህብረተሰቡ ለቴክኒክና ሙያ ያለውን አመለካከት በመቀየር ወጣቱ ወደ ቴክኒክና ሙያ ገብቶ አምራችና ሰርቶ መብላት የሚችል ዜጋ እንዲሆኑ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ
ለሚ ኩራ ኮሚዩኒኬሽን
ጥቅምት 27/2018


.

Copyright © All rights reserved.

Created with