Online Admission ‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ››

‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ››

26th November, 2025

ቀን    ህዳር 15/2018 ዓ/ም


‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ  የፀረ ሙስና ቀን  ተከበረ››


የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ  "ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በኢትዮጵያ ለ21ኛ ጊዜ  የሚከበረውን የፀረ ሙስና ቀን  ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በመርሀ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር የደረጉ የኮሌጁ ዋና ዲን የሆኑት ታደሰ መኮንን( ዶ/ር)   ሲሆኑ በመክፈቻ ንግግራቸው በዛሬው ዕለት  በኮሌጃችን የሚከበረው አለም  አቀፍ  የፀረ-ሙስና ቀን  ትውልድን በስነ-መግባር ማነፅና ተቋምን በአሰራር መገንባት ለአንድ ሀገር እድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው በመግለፅ   ሙስናን  በጋራ በመታገል  ከሙስና  የፀዳች ሃገረ እንድትኖረን  ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት  ብለዋል፡፡
 የኮሌጁ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ዳዊት ተፈሪ የዕለቱን በዓል  በተመለከተ ሰነድ  ለታዳሚዎች አቅርበዋል።
በበዓሉ የሰራተኞች የጥያቄና መልስ ውድድር የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ከአንድ እስከ ሶስት ለወጡ ተወዳደሪዎች የሰርተፍኬት ሽልማት በማበርከት የዕለቱ መርሀ-ግብር ተጠናቋል፡፡
         ‹‹የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን››

.

Copyright © All rights reserved.

Created with