Online Admission ‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ››

‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ››

26th November, 2025

ቀን    ህዳር 16/2018 ዓ/ም


‹‹ ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ  የፀረ ሙስና ቀን  ተከበረ››


የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ  "ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በኢትዮጵያ ለ21ኛ ጊዜ  የሚከበረውን የፀረ ሙስና ቀን  ከሰልጣኞች ጋር በመሆን በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በመርሀ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር የደረጉ የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትዕግስት አይናለም ሲሆኑ በመክፈቻ ንግግራቸው በዛሬው ዕለት  በኮሌጃችን የሚከበረው አለም  አቀፍ  የፀረ-ሙስና ቀን  ትውልድን በስነ-መግባር ማነፅና ተቋምን በአሰራር መገንባት እንዲሁም   ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ ማፍራት የኮሌጁ አንዱ ትልዕኮ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ 
 የኮሌጁ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ዳዊት ተፈሪ የዕለቱን በዓል  በተመለከተ  ገለፃና ማብራሪያ   ለሰልጣኞች አቅርበዋል።
ኮሌጁ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስናን ቀን አስመልክቶ የሰልጣኞች የጥያቄና መልስ ውድድር እና ስፖርታዊ ውድድር የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ከአንድ እስከ ሶስት ለወጡ ተወዳደሪዎች የሰርተፍኬትና የዋንጫ ሽልማቶችን በማበርከት የዕለቱ መርሀ-ግብር ተጠናቋል፡፡
         ‹‹የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን››

.

Copyright © All rights reserved.

Created with