Online Admission የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጅ ሽግግር የስራ ሂደት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ተደራጅተው የሚሰሩ አዲስ ኢንተርፕራይዞችን ርክክብ አደረገ፡፡

የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጅ ሽግግር የስራ ሂደት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ተደራጅተው የሚሰሩ አዲስ ኢንተርፕራይዞችን ርክክብ አደረገ፡፡

26th November, 2025

ቀን ህዳር 16/2018 ዓ/ም


የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጅ ሽግግር የስራ  ሂደት  በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ተደራጅተው የሚሰሩ አዲስ  ኢንተርፕራይዞችን  ርክክብ  አደረገ፡፡


በርክክቡ የኮሌጁ የኢ/ኤ/ ባለሙያዎች፣ ዘርፉን የሚመሩ የክ/ከ ቡድን መሪዎችና የወረዳ ባለሙያዎች ፣  የአ/አ/ የስራና ክህሎት ቢሮ የኢ/ኤ  የሥራ ሂደት  ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ታደለ ሀይሉ ተገኝተዋል።
የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/ም  ዲን የሆኑት ሙሉጌታ አለሙ(ዶ/ር)   ኮሌጁ አዲስ  የተረከባቸውን ኢንተርፕራይዞች  ፍላጎትን መሰረት  ያደረገ በአራቱም የድጋፍ ማዕቀፎች ድጋፍ በማድረግ የኢንተርፕራይዞችን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በርክክቡ ከ300 በላይ አንቀሳቃሾች እንደተገኙና በዛሬው ዕለት  የኢንተርፕሪነርና ካይዘን ስልጠና መስጠት እንደጀመረና ከስልጠናው በኋላ  የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC)  እንደሚወስዱ  የኮሌጁ የኢ/ኤ አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሪት ታደለች ሰሀሌ ገልፀዋል፡፡
‹‹የለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን››

.

Copyright © All rights reserved.

Created with